ከሪል እስቴት አልሚዎች እና ከግለሰቦች በሰነዶች ማረጋገጫ ንብረት ገዝተው ወደመሬት ተቋማት በመቅረብ ስም ያላዞሩና የይዞታ ባለቤትነት ማረጋገጫ ያልያዙ ባለንብረቶች ሂደቱን እንዲያጠናቅቁ የከተማ አስተዳደሩ የመሬት ልማት እና አስተዳደር ጥሪውን አስተላለፈ። ቢሮው ቀደም ባለ ጊዜ በመሬት ላይ ያረፈን ንብረት ተሻሽጠው (ሸጠው/ገዝተው) እስካሁን የስመ-ንብረት ዝውውር ያላደረጉ (የይዞታ ማረጋገጫ) ያልያዙ አካላት በአጭር ጊዜ ሂደቱን እንዲያጠናቅቁ አሳስቧል። የከተማ አስተዳደሩ የመሬት ልማት እና አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ አቶ መኮንን ያኢ የስም ንብረት ዝውውሩ በወቅቱ አለመደረግ ንብረት ገዝተው ነገር ግን የንብረት ባለቤት ማረጋገጫ ያልያዙ ወገኖች ለጉዳት እየዳረገ ነው ብለዋል። የቢሮ ኃላፊው ስለ ስም ንብረት ዝውውር ምንነት ሲናገሩም አንድ ሰው ያፈራውን ንብረት በራሱ ለሌላ ሶስተኛ...